Something About Company
አሚጎስ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር
አሚጎስ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር የተቋቋመው በኢትዮጵያ የኅብረት ሥራ ማኅበር አዋጅ መሠረት በቁጥር 147/1998 ሲሆን ሕጋዊ ሰብእናውን ከአራዳ ክፍለ ከተማ የኅብረት ሥራ ማኅበር ማደራጃ ቢሮ እና ከንግድ ሚኒስቴር በጥር 2005 ዓ.ም. ፍቃድ አግኝቶ በሥራ ላይ ይገኛል። አሚጎስ በቀዳሚነት የሚንቀሳቀሰው የአባላት መደበኛ ቁጠባ እና አክሲዮን በመሰብሰብ የተሻለ የብድር አገልግሎት በማቅረብ የተሳለጡ የማህበራዊ ግንኙነቶች እና ኢኮኖሚያዊ ለውጦች በአባላትና በማህበሩ እንዲኖሩ ማድረግ ነው።
በአሁኑ ሰዓት አሚጎስ ከ2200 በላይ አባላት ሲኖሩት ወደ 70 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ሀብት አለው። በብድር መጠን እስከ 180 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ለ1100 አባላት እስከ አሁን ያቀረበ ሲሆን ከዚህም ውስጥ ብር 90 ሚሊዮን ከ300 በላይ አባል ተበዳሪዎች ጋር በሥራ ላይ ይገኛል። የአባልነት ጥቅም ከፍ ለማድረግ ደግሞ በ650 ሺህ ብር ደግሞ በ5 የተመረጡ ባንኮች አክሲዮን ገዝቶአል።